የኒቆላዊያን አስተምህሮት።


  የራዕይ መጽሐፍ ተከታታይ።

የኒቆላዊያን አስተምህሮት።


William Branham.

ውስጥ ሙሉ መለያ ያንብቡ...
የጴርጋሞንም ቤተ ክርስቲያን ዘመን።

የዮሐንስ ራእይ 2:15,
“እንዲሁየኒቆላውያንን ትምህርት እንደ እነዚህ የሚጠብቁ ሰዎች ከአንተ ጋር ደግሞ አሉ።.”

ኒቆላዊያን የሚለዉ ቃል በኤፌሶን ቤተክርስቲያን ዘመን ላይከሁለት የግሪክ ቃሎች ማለትም ኒቃኦ ወረራ እና ሌኦ ማለትም ምእመን ከሚሉ የመጣ እንደሆኑ መነጋገራችንን ታስታዉሳላችሁስለሆነም ኒቆላዊያን ማለት ‹‹ምእመናኑን መዉረር›› ነዉ፡፡ አሁን ይሄ ጉዳይ ለምንድን ነዉ መጥፎ ነገር የሆነዉ በጣም መጥፎነዉ ምክንያቱም እግዚአብሔር ቤተክርስቲያኑን በተመረጡ የመሪ ጉባኤ እጅ ላይ ያዉም ፖለቲካዊ ሐሳብ ባላቸዉ እጅ ላይአላስቀመጣትም፡፡ እርሱ ቤተክርስቲያንን ያስቀመጠዉ በእግዚአብሔርበተሾሙ፤ በመንፈሱ በተሞሉ፤ ቃሉን በሚኖሩ እና ህዝቡንም ቃሉንእየመገቡ በሚኖሩ ሰዎች ላይ ነዉ፡፡ እርሱ ብዙሀኑ በቅዱስካህናት እንዲመሩ በማለት ህዝቡን በተለያየ እርከን ከፋፍሎ አላስቀመጠም አመራሩ በርግጥ ቅዱስ መሆን እንዳለበት እዉነት ነዉነገር ግን አጠቃላይ ህዝቡም መቀደስ ደግሞ አለበት ከዚም ባለፈ በመጽሐፍ ቅዱስ ዉስጥ ካህናቱም ወይም አገልጋዮች በእግዚአብሔርእና በሰዎች መካከል ሆነዉ የማማለድ ተግባር የሰሩበት ቦታ የለም፡፡ አልያም ደግሞ እነሱ ከሌላዉ ህዝብ ተለይተዉ ለብቻቸዉየአምልኮ ስርአት የሚያደርጉበት ቦታ አይገኝም፡፡ እግዚአብሔር ሁሉን እንዲወዱት እና በአንድነት እንዲያገለግሉት ነዉየሚፈልገዉ፡፡ ኒቆላዊያንነት እነዚህን ሁሉ ተግባራት አጠፋቸዉ እና በእነዚህ አካሔድ ፋንታ አገልጋዮች የሚባሉትን ከህዝቡ ለይቶመሪዎቹን አገልጋዮች መሆን ሲገባቸዉ ተገልጋይ መሪዎች አደረጋቸዉ፡፡አሁን የጉዳዩ እዉነታ ቃሉ ነዉ ‹‹ሽማግሌ›› የሚያመላክተዉየሰዉየዉን ማንነት ነዉ ‹‹ጳጳስ›› የሚለዉ ቃል የዛን የእራሱን የሰዉየዉን የአገልግሎት አይነት ያመለክታል ሽማግሌ ሰዉ ነዉጳጳስነት ደግሞ የሰዉየዉ የአገልግሎት ድርሻ ነዉ ፡፡ ‹‹ሽማግሌ›› የሚለዉ ቃል ሁልጊዜም ያመለክት የነበረዉ ወደ ፊትምሊያመላክት የሚችለዉ የሰዉየዉን በጌታ ቤት ሆኖ ያሳለፈዉን የጊዜ እርዝመት ነዉ ሽማግሌ የሆነበት ምክንያት ስለተመረጠ ወይምስለተሾመ ብቻ ሳይሆን እርሱ በእድሜም ገፋ ያለ ብዙ ዘመናትን ያሳለፈ ልምድ ያለዉ ከልምዱም የተነሳ አስተማማኝ በክርስትናጉዞዉም ጸንቶ በመቆየት ማረጋገጥ የቻለ መሆኑን ነዉ፡፡ ነገርግን ጳጳሶቹ ጳዉሎስን አልተከተሉም እንዲያዉም ጳዉሎስ በሐዋርያት ስራ 20 ላይ እንደተገለጸዉ በቁጥር 17 ላይ ሽማግሌዎች እንደተጠሩ እና ቁጥር 28 ላይጠቆጣጣሪዎች(ጳጳሳት) ተብለዉ እንደተጠሩ ተጽፋል፡፡ እናም እነኚህ ጳጳሶች (የፖለቲካ ሐሳብ ያላቸዉ እና የሀይል ጥማት ያላቸዉእንደሆኑ ጥርጥር የለዉም) ጳዉሎስ ተቆጣጣሪዎች አድርጎ የሾማቸዉ በነበሩበት አጥብያ ቤተክርስቲያን ብቻ የነበረ ቡሆንም ለእነሱግን ጳጳስ ማለት በብዙ የአጥቢያ ቤተክርስቲያናት አመራር ላይ የተሸመ ስልጣን ያላቸዉ አድርገዉ ነዉ ያስቀመጡት ይሄ አይነቱአስተሳሰብ ደግሞ በመጸሐፍ ቅዱስም ሆነ በታሪክ ላይ አይገኝም፡፡ ስለሆነም ይሄ በመጀመሪያዉ ዘመን ይተገበር የነበረዉ ተግባርበአሁን ሰአት ራሱን የቻለ አስተምህሮት ሆኖ መጣ፡፡ በአሁን ሰአት ያሉ ጳጳሶች ሰዉን ሁሉ መቆጣጠር እና እንደ ፍላጎቶቻቸዉመምራት እንችላለን ብለዉ ያባሉ አሁን በርግጥ ይሄ አስተምህሮት ተግባሩ የተጀመረዉበመጀመሪያዉ ዘመን ነበር፡፡ ትልቁ ችግር ያረፈዉ አሁን በሁለት ቃሎች ላይ ነዉ ሽማግሌዎች( ) እና ጠባቂዎች(ጳጳስ) ምንም እንካን መጽሐፍ ቅዱስ ላይበየቤተክርስቲያን ዘመን ላይ ብዙ ሽማግሌዎች እንደነበሩ ቢያሳይም አንዳንዶቹ (በመካከላቸዉ አንዳቸዉ በሌላቸዉ ላይ) መነሳሳትጀመሩ ጰጳስ የመሆኑ ሀሳብ የበላይ ወይም ስልጣን የማግኘት እንደሆነ በማሰብ፡፡

ይሄም ደግሞ ‹‹እኔ ለ አገልግሎቴ የለየኃቸዉን ጳዉሎስ እና በርናባስን ለአገልግሎቴለዩልኝ›› የሚለዉን በመንፈስ ቅዱስ የሚደረገዉን ምሪት ይክዳል፡፡ ይሄ የቃሉ ተቃዋሚነት እና የክርስቶስ ተቃዋሚነት ነዉ፡፡ማቴ 20፡25-28 ኢየሱስ ግን ወደ እርሱ ጠርቶ እንዲህ አላቸው፦ የአሕዛብ አለቆች እንዲገዙአቸው ታላላቆቹም በላያቸው እንዲሠለጥኑ ታውቃላችሁ። በእናንተስ እንዲህ አይደለም፤ ነገር ግን ማንም ከእናንተ ታላቅ ሊሆን የሚወድ የእናንተ አገልጋይ ይሁን፥ ከእናንተም ማንም ፊተኛ ሊሆን የሚወድ የእናንተ ባሪያ ይሁን፤ እንዲሁም የሰው ልጅ ሊያገለግል ነፍሱንም ለብዙዎች ቤዛ ሊሰጥ እንጂ እንዲያገለግሉት አልመጣም።” ማቴ 23:8-9, “እናንተ ግን፦ መምህር ተብላችሁ አትጠሩ፤ መምህራችሁ አንድ ስለ ሆነ እናንተም ሁላችሁ ወንድማማች ናችሁ። አባታችሁ አንዱ እርሱም የሰማዩ ነውና በምድር ላይ ማንንም፦ አባት ብላችሁ አትጥሩ።”

ይሄን ጉዳይ እንዲያዉም የበለጠ ለማብራራት ኒቆላዊያንነትንበዚህ መንገድ እስኪ ላብራራዉ በራእይ 13፡3 ላይ ያለዉን ታስታዉሳላችሁ ‹‹ከራሶቹም ለሞት እንደ ታረደ ሆኖ አንዱን አየሁ፥ ለሞቱ የሆነውም ቍስል ተፈወሰ። ምድርምሁሉ አውሬውን እየተከተለ ተደነቀ፥›› አሁን ቆስሎ የነበረዉ ራስየጣኦት አምላኪዉ የሮም ግዛት እንደነበረ አዉቀናል ያ ታላቁ የፖለቲካዊ የአለም ገዢ ይሄም ራስ ዳግም ‹‹ በሮም የካቶሊክ መንፈሳዊአገዛዝነት›› መልክ አንሰራርቶ ተነሳ፡፡ አሁን ይሄን በጥንቃቄ ተመልከቱት የጣኦት አምላኪዉ የሮም ፖለቲካ ለስኬት የሚሆን ነገርምን አደረገች ‹‹ከፋፍላ ወረረች›› ይሄ የሮም ዘር ነዉ ከፋፍሎ መዉረር የብረት ጥርሶቿ ታደቅቃቸዋለች በጥርሷ ያደቀቀቻቸዉ ሁሉዳግም አይነሱም ይሄዉም ተመሳሳይ የብረት ዘር ያኔ የሐሰተኛ ቤተክርስቲያን ሆና ስትነሳ በነበረ ጊዜ ከእርሷ ጋር አብሮ ስለቀረፖሊሲዋም ተመሳሳይ ነዉ መከፋፈል እና መዉረር ይሄ ነዉ ኒቆላዊነት እግዚአብሔርም አብዝቶ ይጠላዋል፡፡

አሁን በታሪክም በደንብ ማወቅ እንደሚቻለዉ ይሄ የተሳሳተሐሳብ ወደ ቤተክርስቲያን ሾልኮ ከገባ በኃላ ብዙ ሰዎች የጳጳስነትን ስራ ወደ መስራት አዘነበሉ ምክንያቱም ይሄ ስልጣን በደንብለተማሩ እና ቁሳዊ ብልጽግናን ለሚፈልጉ እና ፖለቲካዊ አስተሳሰብ ላላቸዉ ሰዎች የሚሰጥ መሆኑ ስለታወቀ ከዚህም የተነሳ የሰዉጥበብ እና ሀሳብ የመለኮትን ጥበብ እና ሐሳብ እንዲሁም የመንፈስ ቅዱስን የበላይ ተቆጣጣሪነትን ማስቀረት ጀመረ ይሄ በርግጥአሳዛኝ ክፋት ነዉ ጳጳሳቶቹ ቃሉን ለማገልገል የሚታይ የክርስትና ባህሪን ማሳየት አስፈላጊ እንዳልሆነ አድርገዉ ሲቀጥሉ ዋናዉየሚቆጠረዉ የቤተክርስቲያኑን ስነ ስርአቶች እና በአላቶች መተግበር ብቻ እንደሆነ ማሳየታቸዉ ይሄ ለክፉ ሰዎች(አማላዮች)መንጋዉን እንዲመሩት በር ከፈተ፡፡

ሰዉ ወራሽ በሆነ አስተምህሮት የጳጳሶችመጽሀፍቅዱሳዊ ባልሆነ ባልተሰጣቸዉ ስፍራ ላይ ከፍ ማለት መጀመር ቀጣዩ ደረጃ የሆነዉ ለልዩ ልዩ የሐይማኖታዊ የስልጣን ተዋረድስያሜዎችን መስጠት ነዉ በቅርቡም በጳጳሶች ላይ የተሸሙ ሊቀ ጳጳሳት በሊቀ ጳጳሶች ላይ ደግሞ ብጹእ አቢያት የሚሉ ስያሜዎችተመሰረቱ ሶስተኛዉ ቦኒፌስ በነበረ ጊዜ በሁሉም ላይ የተሸመ ጳጳስ ነበር፡፡

የኒቆላዊያን አስተምህሮት እና የክርስትና እምነት ከባቢሎናዊያን ጋርመቀላቀል ያመጣዉ ዉጤት በእዝቄል ምእራፍ 8፡10 ላይ እንደተገለጸዉ ነዉ፡፡ “እኔም ገባሁና እነሆ፥በግንቡ ዙሪያ ላይ የተንቀሳቃሾችና የርኩሳን አራዊት ምሳሌ የእስራኤልንም ቤት ጣዖታት ሁሉ ተስለው አየሁ።” ራዕይ 18:2, “በብርቱም ድምፅ፦ ታላቂቱ ባቢሎን ወደቀች፥ ወደቀች፥ የአጋንንትም ማደሪያ ሆነች፥ የርኵሳንም መናፍስት ሁሉ መጠጊያ የርኵሳንናየተጠሉም ወፎች ሁሉ መጠጊያ ሆነች፤”

አሁን ይሄ የኒቆላዊያን አስተምህሮት በቤተክርስቲያን ዉስጥ የተመሰረተዉ ህግ ህዝቡ የቀድሞ ቅዱሳን መጻህፍትንያነብ ስለነበር ያን ያህል በደንብ ዘልቆ አልገባም ነበር ስለዚህ ቤተክርስቲያን ምን አደረገች ጻድቃን የነበሩትንየአስተማሪዎችን ጽሁፎች አቃጥላ አስወገደችዉ እናም እንዲህ ይላሉ ‹‹ ቃሉን ለማንበብ እና ለመረዳት የተለየ ትምህርትያስፈልጋል ጴጥሮስ እራሱ ጳዉሎስ የጻፋቸዉን ብዙ ነገሮች ለመረዳት ያስቸግራል አለ›› ስለሆነም ቃሉን ከህዝቡ ካስወገዱ በኃላሕዝቡ ካህናቶቹ የሚነግሯቸዉን ብቻ ማዳመጥ እና አድርጉ የተባሉትን ብቻ ማድረግ ጀመሩ እግዚአብሔር እና ቅዱስ ቃሉ ብለዉ ይጠራሉ፡፡የሕዝቡን አእምሮ እና አኗኗር ወስደዉ ጨቋኝ በሆነዉ የክህነት አገዛዝ ስር ባሪያዎች እንዲሆኑ አደረጉ፡፡

አሁን የካቶሊክ ቤተክርስቲያን የሰዎችንአእምሮ እና አናናር እንደምትፈልግ ማረጋገጥ ከፈለጋችሁ በቲኦዶሲየስ ኤክስ የታወጀዉን አዋጅ ማዳመጥ ትችላላችሁ፡፡

ይሄ አዋጅ በመጀመሪያዋ የሮም ቤተክርስቲያን ከተጠመቀ በኃላ ነዉ ወዲያዉኑ የወጣዉ ‹‹ እኛ ሶስት ንጉሰ ነገስታትበቅዱስ ጴጥሮስ በኩል ለሮም የደረሰዉን ሐይማኖት በታማኝነት ባህላችን አድርገን የጠበቅነዉን እና አሁን ከሮም ዳማሰስ በሆነዉፖንቲፍ እና የአሌክሳንድርያዉ ጴጥሮስ የጴርጋሞንም ቤተ ክርስቲያን ዘመን 19 በወንጌላት መጻህፍት እና በሐዋርያት ተቋም ቅዱስ ሐዋርያ በሆነዉ የታወጀዉን ማለትምበአብ፤በወልድ፤በመንፈስ ቅዱስ አንድ አምላክነት በቅዱስ ስላሴ እኩል ክብርነት እናምናለን፡፡ ይሄንን የፖለቲካዊ እምነት ተከታይካቶሊክ ክርስቲያን ብለን እንጠራዋለን፡፡ የሌሎችን ትርጉም የለሽ ትርጉም የማይሰጥ አስከፊ ሐይማኖት ተከታዮችን መናፍቃዊያንንእና በቤተክርስቲያን ስም የሚያደርጉትን ስብሰባ እንቃወማለን እንከለክላለን የመለኮታዊ ከሆነዉ የኩነኔ ፍርድ ባሻገርም ሰማያዊበሆነዉ ጥበብ በስልጣናችን የምንጥልባቸዉን ከባድ ቅጣት መጠበቅ አለባቸዉ፡፡፡››

ይሄ ንጉሰ ነገስት ያወጣዉ አስራ አምስተኛዉ የህግቅጣት ለብዙ አመታት ወንጌላዊያንን ሐይማኖታዊ እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ ፤መሰረታዊ የሰዉ መብታቸዉን እንዳይጠቀሙ እናም በተለያዩገንዘብ ቅጣት፤ እንዲወረስባቸዉ በማድረግ፤ እንዲወገዱ በአንዳንድ ጉዳዮች ላይም የሞት ቅጣት እንዲቀጡ ማድረግ ነበር፡፡ ምን እንደሆነ ታዉቃላችሁ? ዛሬም ቢሆን ወደዚሁ አይነት መንገድእየገባን ነዉ፡፡

የሮም ካቶሊክ ቤተክርስቲያን እራሷን እናት ቤተክርስቲያን ብላ ትጠራለች እራሷን የመጀመሪያዋ ወይም ቀዳሚዋቤተክርስቲያን ብላ ትጠራለች ይሄም ሙሉ በሙሉ ትክክል ነዉ፡፡ ወደ ኃላ አፈግፍጋ ወደ ሐጥያት የገባች የመጀመሪያዋ የሮም ቤተክርስቲያንነች፡፡ እራሷን በማደራጀት ቀዳሚዋ ነች፡፡ የኒቆላዊያንነት ስራ እና አስተምህሮት የተገኘባት ቤተክርስቲያን ናት፡፡ ማንም ሰዉእናት መሆኗን አይክድም፡፡ እናት በመሆኗም ልጆችን አፍራታለች፡፡ልጅ የሚወለደዉ ከሴት ነዉ፡፡ በሮም ሰባት ተራራዎች መካከል በቀይ መጎናጸፊያ ተጎናጽፋ ተቀምጣለች፡፡ እሷ ጋለሞታ ነች እናምልጆች አሉዋት እነዚህ ልጆቿም ከእርሱዋ ወጥተዉ እራሳቸዉን በማደራጀት ወደ ኒቆላዊያን አስተምህሮት የተመለሱ የፕሮቴስታንትቤተክርስቲያናት ናቸዉ፡፡ ይህች ልጆች ያሏት እናት ቤተክርስቲያን ጋለሞታ ትባላለች፡፡ እንዲህ አይነታ ሴት ለጋብቻዋ እዉነተኛያልሆነች ነች አስቀድማ ከእግዚአብሔር ጋር ተጋብታ ነበር ነገርግን ከዛ ወጥታ ከዲያብሎስ ጋር አመነዘረች በምንዝርናዋም የተነሳ እንደ እሷ አመንዝራ የሆኑ ልጆችን አፈራች፡፡ እነዚህ የእናትእና ልጆች ጥምረት ጸረ-ቃል፤ጸረ-መንፈስ እናም ዉጤቱ ጸረ-ክርስቶስ መሆን ነዉ፡፡ አዎ ጸረ-ክርስቶስ፡፡

አሁን ብዙም እርቄ ከመሄዴ በፊት እነዚህ የቀደምት ጳጳሳት እነሱ ከቃሉም በላይ የሆኑ አድርገዉ እንደሚሰማቸዉለመግለጽ እፈልጋለሁ፡፡ ለሕዝቡ ወደ እነሱ መጥተዉ ሐጥያታቸዉን ቢናዘዙ ይቅርታን መስጠት እንደሚችሉ አድርገዉ ይነግሯቸዋል፡፡ በሁለተኛዉመቶ ክፍለዘመንም ጨቅላ ሕጻናትን ማጥመቅ ጀመሩ በርግጥ የዳግም ዉልደትን ጥምቀት እየተለማመዱ ነዉ፡፡ ይሄ ፈጽሞ እዉነት ሊሆንአይችልም፡፡ ሰዎች በአሁን ሰአት የተደባለቁ መሆኑ አያስደንቅም፡፡ ከተዳባለቁ እና ከጴንጤቆስጣዊያን ጋር ከተቀራረቡ አሁንከ2000 አመታት በኃላ ከነበረዉ የመጀመሪያ እዉነት በመራቃቸዉ አሳዛኝ ሁኔታ ዉስጥ ገብተዋል ማለት ነዉ፡፡

ኦ፡ የእግዚአብሔር ቤተክርስቲያናት አንድ ተስፋ ብቻ አለ ወደ ቃሉ ተመለሱእና

ውስጥ ሙሉ መለያ ያንብቡ...
የጴርጋሞንም ቤተ ክርስቲያን ዘመን።


የክርስቶስ ምሥጢር
ተከታታይ።

የእንግሊዝኛ ጋዜጣ ድረ።

እግዚአብሔር እና ሳይንስ
ተከታታይ ኢንዴክስ።

በራእይ መጽሐፍ ላይ።

 

ጥሩ ዜናው።
ኢየሱስም ስለ ኃጢአታችን ሞቷል።

የውኃ ጥምቀት።
መንገዱ ይህ ነው.
በእርሱ ሂድ.

የመለኮት ገልጿል።

 

መልእክት ዋና ዋና ትምህርቶች።

ከተፈጥሮ በላይ ደመና።

የእሳት ዓምድ።

መቃብሩ ባዶ ነው።
እርሱ ሕያው ነው።

አርኪኦሎጂ።
ሰዶምና ገሞራ።

የመኖር ቃል ተከታታይ።

 

የእሳት ዓምድ።
የመለኮት አብራርቷል።

የማብቂያ ጊዜ ተከታታይ።

 

የኖህ መርከብ።

ወቅታዊ ምርምር።
ጋብቻ እና ፍቺ።
ክርስቲያን የእግር ጉዞ
ተከታታይ። - ምልክት።

ሚቶሎጂ። ባቢሎን የምንጭ።

የመጀመሪያው ኃጢአት።
አንድ አፕል ማለት ነው?።

በለዓም መሠረተ ትምህርት ነው።

እንደሆነ ሴት ኤልዛቤልን።

የእኛ ዕድሜ በሎዶቅያ።

 
 

የእሱ ቤተ ክርስቲያን ከኢየሩሳሌም ውጪ የሚኖሩ ክርስቶስ ነው።

የኒቆላውያንን ትምህርተ።

የፍጥሞ ራዕይ።

 

ሚስጥራዊ ባቢሎን።

ሰባት ማኅተሞች
ተከታታይ።

የመልእክታችን ዝርዝር።

የገና ተከታታይ።

  ቅዱስ መጽሐፉ እንዲህ ይላል...

ከዚያ ወራት በኋላ ከእስራኤል ቤት ጋር የምገባው ቃል ኪዳን ይህ ነውና ይላል ጌታ፤ ሕጌን በልቡናቸው አኖራለሁ በልባቸውም እጽፈዋለሁ፥ እኔም አምላክ እሆንላቸዋለሁ እነርሱም ሕዝብ ይሆኑልኛል።

ወደ ዕብራውያን 8:10


ሙሉ መጠን ሥዕሎች ወይም ፒዲኤፍ ለማውረድ ምስል ላይ ጠቅ ያድርጉ።


Acts of the Prophet.

(PDF እንግሊዝኛ)።

The Two Babylons

by Rev Alexander Hislop.
(PDF እንግሊዝኛ)።

ቻይና ውስጥ በረዶ ውስጥ አንዲት ተራራ እና የጽጌረዳን።

የእሳት በአበቦች።

የእሳት ዓምድ።
- የሂዩስተን 1950።

አንድ ፒራሚድ ዓለት ላይ ብርሃን ነው።

እግዚአብሔር ብዙ
ስያሜዎች...
ነገር ግን አንድ
የሰዉ ስም
አለዉ ያም
ስምኢየሱስ ነዉ፡፡



መልዕክት ሃብ...ቋንቋዎን ይምረጡ. ወንድም ብራናም ነፃ መልዕክቶችን የውርድ።


የራዕይ መጽሐፍ ተከታታይ።
በሚቀጥለው ገጽ ላይ ይቀጥላል።
(የበልዓም ትምህርት።)