የመጀመሪያው ኃጢአት። የሕይወት ዛፍ።


  የራዕይ መጽሐፍ ተከታታይ።

የመጀመሪያው ኃጢአት። ፖም ነበር?
(የእባቡ ዘር ታሪክ።)


William Branham.

ውስጥ ሙሉ መለያ ያንብቡ...
የኤፌሶን ቤተክርስቲያን ዘመን።

ራእይ 2:7,
“...ድል ለነሣው በእግዚአብሔር ገነት ካለው ከሕይወት ዛፍ እንዲበላእሰጠዋለሁ።”

ይሄ በሁሉም ዘመናት ድል ለሚነሱ ሁሉየተገባ ሽልማት ነዉ የመጨረሻዉ የትግል ድምጽ ሲያበቃ ጦርነታችን ሲያበቃ ከዚያ በእግዚአብሔር ገነት እናርፋለን ድርሻችንምለዘላለም ከህይወት ዛፍ መካፈል ይሆናል፡፡

“ከሕይወትዛፍ” ይህ ደስ የሚል ንግግር አይደለምን ይሔ ቃልበዘፍጥረት መጽሐፍ ሶስት ጊዜ እንዲሁም በራእይ መጽሐፍ ሶስት ጊዜ ተገልጿል በስድስቱም ቦታዎች ሁሉ ላይ አንድ አይነት ዛፍሲሆን የሚያመለክተዉም አንድ ነገር ነዉ፡፡

ነገር ግን የሕይወት ዛፍ ማን ነዉ? ደህና በመጀመሪያ ዛፍ የሚለዉ ቃል ምንን እንደሚያመለክት ማወቅ አለብን በዘሁልቁ24፡6 ላይ በልአም እስራኤልን በገለጸበት መልኩ “በውኃም ዳር እንዳሉ ዝግባዎች ተዘርግተዋል።” ዛፎች በመጽሐፍ ቅዱስ ዉስጥ በጠቅላላ አንድ አካልን የሚጠቁሙ ናቸዉ መዝሙር 1 ስለዚህየሕይወት ዛፍ አንድ ህይወት ያለዉ አካል መሆን አለበት እርሱም ኢየሱስ ነዉ፡፡

አሁን በኤደን ገነት ዉስጥ ሁለት የቆሙ ዛፎች ነበሩ አንደኛዉ የህይወት ዛፍሲሆን ሌላኛዉ መልካም እና ክፉን የሚያሳዉቀዉ ዛፍ ነዉ ሰዉ የተፈጠረዉ በህይወት ዛፍ እንዲኖር ነበር ሌላኛዉን ዛፍ ግንመንካት የለበትም ካልሆነ ግን ይሞታል ነገር ግን ሰዉ ከሌላኛዉ ዛፍ ተካፈለ እና በሀጥያቱ ምክንያት ሞተ ከእግዚአብሔርም ጋርተለያየ፡፡

አሁን ያኔ በኤደን ገነት ዉስጥ የነበረዉ ዛፍ የህይወት ዛፍ የነበረዉ ኢየሱስነዉ፡፡ በዮሐንስ ወንጌል ከምእራፍ ስድስት እስከ ስምንት ባለዉ ክፍል ኢየሱስ እራሱን የዘላለም ህይወት ምንጭ አድርጎአስቀምጧል እራሱን ከሰማይ የወረደ መና ብሎ ጠርቷል እራሱን አሳልፎ እንደሚሰጥ እና ማንም ሰዉ እሱን የሚበላ ሁሉ እንደማይሞትተናግሯል፡፡ አብርሃምን እንደሚያዉቀዉ እና ከአብርሀም በፌት እንደነበረ ተናግሯል፡፡ እርሱ እራሱ የህይወትን ዉሃ እንደሚሰጥእና ሰዉ ከእርሱ ከጠጣ ለዘላለም እንደሚኖር እና ዳግም እንደማይጠማ አሳዉቋል፡፡ እርሱ ታላቁ እኔ ነኝ አምላክ እንደሆነአሳይቷል፡፡ እርሱ የህይወት እንጀራ ፤ የህይወት ምንጭ፤ዘላለማዊ የህይወት ዛፍ ነዉ፡፡ በእግዚአብሔር ገነት እንደሚኖረዉ ሁሉእርሱ ያኔ በኤደን ገነት መካከልም ነበር፡፡

አንዳንዶች በኤደን ገነትዉስጥ የነበሩት ሁለቱ ዛፎች እግዚአብሔር እንደፈጠራቸዉ እንደማንኛዉም አይነትዛፎች ናቸዉ የሚሉ አሉ ነገር ግን ተማሪዎች በጥንቃቄ እንዲህ እንዳልሆነ ያዉቃሉ፡፡ መጥምቁ ዮሐንስ ከዛፍ ስር ምሳር ተቀምጧልብሎ ሲናገር ስለመንፈሳዊ መመሪያ ነዉ እንጂ ስለ ተፈጥሮ ዛፍ አልነበረም ያወራ የነበረዉ፡፡ አሁን 1 ዮሐንስ 5፡11 እንዲህ ይላል,

“ እግዚአብሔርም የዘላለምን ሕይወት እንደ ሰጠን ይህም ሕይወትበልጁ እንዳለ ምስክሩ ይህ ነው።.”

ኢየሱስምበዮሐንስ 5:40,እንዲህ አለ
“ነገር ግን ሕይወት እንዲሆንላችሁ ወደ እኔ ልትመጡ አትወዱም።.”

የእግዚአብሔር ቃል መዝገብ በግልጽ ሕይወት ዘላለማዊህይወት በልጁ እንዳለ ይናገራል ሌላ ቦታ የለም፡፡

I ዮሐንስ5:12,
“ልጁ ያለው ሕይወት አለው፤ የእግዚአብሔር ልጅ የሌለው ሕይወትየለውም።”አሁን የተጻፈዉ ነገር ስለማይቀየር በላዩላይ መጨመርም ሆነ መቀነስ ስለማይቻል ህይወት በልጁ ብቻ እንዳለ የተጻፈዉ ሁሉ ይመሰክራል ይህም ስለሆነ በኤደን ገነትዉስጥየነበረዉ ዛፍ ኢየሱስ ነዉ፡፡ እሺየሕይወት ዛፍ የተባለዉ ስብእና ያለዉ አካል ከሆነ መልካምእና ክፉዉንየሚያሳዉቀዉም ዛፍ ሌላ ስብእና ያለዉ አካል ነዉ ማለት ነዉ ሌላ ምንም ሊሆን አይችልም፡፡ ጻድቅና ክፉዉ በዛዉ በኤደን ገነትመሀል ጎን ለጎን ቆመዋል ህዝቄል 28:13a
“በእግዚአብሔር ገነት (ሴይጣን) በዔድን ነበርህ.”

ስለ እባብ ዘር በተመለከተም እዉነተኛ የሆነ መገለጥ እናገኛለን በኤደን ገነት ዉስጥ የተከናወነዉ ነገር ይህ ነዉ ቃሉሔዋን በእባቡ እንደተማረከች ይናገራል በትክክል የሆነዉም ከእባቡ ጋር ተዳርታለች፡፡

ዘፍጥረት3:1,እንዲህ ይላል
“እባብም እግዚአብሔር አምላክ ከፈጠረው ከምድር አውሬ ሁሉ ይልቅተንኰለኛ ነበረ።”

ይህ አዉሬ ከሰዉ ጋር በጣም የሚመሳሰል ነዉ(ነገርግን እንስሳ ነዉ) ማሰብ እና ማዉራት የሚችል በዝንጀሮ ዝርያ አይነት እና በሰዉ መካከል ያለ ቆሞ መሔድ የሚችል ፍጥረት ሆኖነገር ግን ወደ ሰዉ ቀረብ ይላል፡፡ እንደሰዉ ዘሩ ከሴት ጋር ተደባልቆ ሰዉ መሆን የሚችል እዲሁም እንድትጸንስ ሊያደርጋትየሚችል ነዉ፡፡ ይህም በተፈጠረ ጊዜ እግዚአብሔር እባብን እረገመዉ ከዚህም የተነሳ የአካሉ ክፍሎች ሁሉ አጥንቶቹን ሁሉቀያየራቸዉና አሁን እንዳለዉ አይነት እባብ በሆዱ እየተንከባለለ መሄድ ጀመረ፡፡ ሳይንስ የቻለዉን ሁሉ ሞከረ ሆኖም ግን በሰዉእና በእንሰሳ መሀል ያለዉ ግንኙነት መያያዝ ምን ላይ እንደሆነ ማግኘት አልቻለም፡፡ እግዚአብሔር ይሄን ተመልክቶታል ሰዉ ደግሞጠቢብ ስለሆነ በሰዉ እና በእንስሳ መካከል አንዳች ግንኙነት እንዳለ ያዉቃል ይህንንም ደግሞ በዝግመተ ለዉጥ ምርምር ለማረጋገጥይሞክራል ዝግመተ ለዉጥ የሚባል ነገር የለም ነገር ግን ሰዉ እና እንሰሳ ሊቀላቀል ይችላል፡፡ እስከዛሬ ድረስ ተሰዉሮ ከነበሩየእግዚአብሔር ሚስጥራቶች መካከል አንዱ ይሄ ነዉ አሁን ግን ተገልጧል ያኔ በኤደን ገነት መካከል ሔዋን ከህይወት ይልቅ ሞትንስትመረጥ የተከናወነ ነገር ነዉ፡፡

አስታዉሱ እግዚአብሔር በኤደን ገነት ዉስጥ ምን እንዳላቸዉ ዘፍጥረት 3፡15
“በአንተና በሴቲቱ መካከል፥ በዘርህና በዘርዋም መካከል ጠላትነትንአደርጋለሁ፤ እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል፥ አንተም ሰኰናውን ትቀጠቅጣለህ።”

ለቃሉ ትኩረት ከሰጠነዉ ሴቲቱ ዘር አላት በርግጥም እባቡም ደግሞ ዘር አለዉ የሴቲቱዘር ከሰዉ የተወለደ ዘር ከሆነ የእባቡም ዘር በተመሳሳይ መልኩ ይሆናል እናም ከሰዉ ወንድ ያልሆነ ሌላ ወንድ ልጅ ይወለዳልማለት ነዉ በሰዎች ጾታዊ ግንኙነት ያልሆነ በእግዚአብሔር አሰራር የተፈጠረ የሴቷ ዘር የክርስቶስ ዘር እንደሆነ የማያዉቅ ተማሬየለም እንዲሁም ደግሞ የእባብ እራስ የሚቀጠቀጥበት ትንበያ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሆኖ የሚያከናዉነዉ ስራ እንደሆነ ሁሉምያዉቃል፡፡ በመስቀሉ ላይ የሴይጣንን እራስ ይቀጠቅጣል ሴይጣን ደግሞ የጌታን ሰኮና ይቀጠቅጣል፡፡

ይሔ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል በምድር ላይ ይህ የሚታየዉ አካላዊዉ የእባባ ዘር እንዴት ወደ ምድር እንደታየየሚያስረዳ መገለጥ ነዉ፡፡ ሉቃ 1፡ 26-35 ላይ ያለዉን እንኳን ስንመለከተዉ ያለምንም አይነት የወንድ ግንኙነት እንዴትየሴቲቱ ዘር በአካል ሊገለጥ እንደቻለ ያሳየናል፡፡ “ በስድስተኛውም ወር መልአኩ ገብርኤል ናዝሬት ወደምትባል ወደ ገሊላ ከተማ፥

ከዳዊት ወገን ለሆነው ዮሴፍ ለሚባል ሰው ወደ ታጨች ወደ አንዲት ድንግል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ፥ የድንግሊቱም ስም ማርያም ነበረ።
መልአኩም ወደ እርስዋ ገብቶ፦ ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ አላት።
እርስዋም ባየችው ጊዜ ከንግግሩ በጣም ደነገጠችና፦ ይህ እንዴት ያለ ሰላምታ ነው? ብላ አሰበች።
መልአኩም እንዲህ አላት፦ ማርያም ሆይ፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋ አግኝተሻልና አትፍሪ።
እነሆም፥ ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፥ ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ።
እርሱ ታላቅ ይሆናል የልዑል ልጅም ይባላል፥ ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል፤ በያዕቆብ ቤትም ላይ ለዘለላም ይነግሣል፥ ለመንግሥቱም መጨረሻ የለውም።
ማርያምም መልአኩን፦ ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆናል? አለችው።

መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት፦ መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል። “ ልክ የሴቲቱ ዘር እግዚአብሔር እራሱን በሰዉ ስጋ ዉስጥ ያባዛበት መንገድ ሲሆን የእባብዘር ደግሞ ሴይጣንም ወደ ሰዉ ዘር መግቢያ ለራሱ በርን መክፈት የቻለበት ቀጥተኛ መንገድ ነዉ፡፡ ለሰይጣን(የተፈጠረ የሆነስብእና ያለዉ መንፈስ ብቻ) በመሆኑ እግዚአብሔር እራሱን ባባዛበት መንገድ ማባዛት ፈጽሞ አይቻለዉም ስለዚህ የዘፍጥረት መጽሐፍእንዴት አድርጎ እራሱን እንዳስተዋወቀ ወይም ወደ ሰዎች ዘር እራሱን እንዴት እንዳባዛ ያሳያል፡፡ ያ የእርሱ ዘር ነበረ ወደሰዉ ዘር የተገናኘዉ፡፡

አዳም ከሔዋን ጋር ጾታዊ ግንኙነት ከማወቁ በፊት እባብ ይህን አስቀድሞ ያዉቅ ነበር በዚህም አማካኝነት ከእርሱየተወለደዉ ልጅ ቃየን ነዉ፡፡ ቃየን (የተወለደዉ የተገኘዉ) “ከክፉው” እንደ ነበረ 1ዮሐንስ 3፡12 በዮሐንስ ላይ የነበረዉ መንፈስ የትኛዉም ስፍራ ላይ አዳምን “ከክፉ” እንደሆነ ብሎ አልጠራዉም(የቃየን አባት ቢሆን ኖሮ እሱምይጠራ የነበረዉ እንደዛ ስለሆነ) በሌላ ስፍራ ግን አዳም “የእግዚአብሔርልጅ” ተብሎ ተገልጿል በአፈጣጠሩም በርግጥ እንደዛዉ ነበር ሉቃስ3፡38፡፡ የቃየን ባህሪ ግን ልክ እንደአባቱ መሆን ጀመረ የሞት አምጪ፤ ነፍሰ ገዳይ፤ በዘፍጥረት 4፡ 5፤9፤13፤14 ላይም ፍጹም የሰዉኛባህሪ እንዳልነበረዉ ያሳያል እንዲያዉም እግዚአብሔር በቃሉ ዉስጥ ስለ ሴይጣን ባህሪ የተናገራቸዉን ነገሮች ጠቅላላ ተመሳሳይ ሆኖእናየዋለን፡፡

“ወደ ቃየንና ወደ መሥዋዕቱ ግን አልተመለከተም። ቃየንም እጅግተናደደ ፊቱም ጠቆረ።
እግዚአብሔርምቃየንን አለው፦ ወንድምህ አቤል ወዴት ነው? እርሱም አለ፦ አላውቅም የወንድሜ ጠባቂው እኔ ነኝን?
ቃየንምእግዚአብሔርን አለው፦ ኃጢአቴ ልሸከማት የማልችላት ታላቅ ናት።እነሆ ዛሬ ከምድር ፊት አሳደድኸኝ፤ ከፊትህም እሰወራለሁ፤ በምድርም ላይ ኰብላይናተቅበዝባዥ እሆናለሁ፤ የሚያገኘኝም ሁሉ ይገድለኛል።“ የቃየን፤የአቤልናየሴትን ትዉልድ ሐረግ አቀማመጥ ትክክለኛ መንገድ በደንብ አስተዉሉት

ዘፍጥረት 4:1,
“አዳምም ሚስቱን ሔዋንን አወቀ፤ ፀነሰችም፥ ቃየንንም ወለደች።እርስዋም፦ ወንድ ልጅ ከእግዚአብሔር አገኘሁ አለች።” ዘፍጥረት4:25,
“አዳም ደግሞ ሚስቱን አወቀ፤ ወንድ ልጅንም ወለደች። ስሙንም፦ቃየን በገደለው በአቤል ፋንታ እግዚአብሔር ሌላ ዘር ተክቶልኛል ስትል ሴት አለችው።..”

ከሁለቱየአዳም ጾታዊ ግንኙነት በኃላ የተወለዱ ሶስት ልጆች አሉ መጽሐፍ ቅዱስ ፍጹም እና ትክክለኛ ስለሆነ ምንም ስህተት የለዉምእንዲበራልን ያህል እንጂ ሶስት ልጆች ከሁለት ጊዜ የአዳም ሔዋንን የማወቅ ተግባር ከተወለዱ ቀና ሆነን ካሰብነዉ ከሶስቱ አንዱከአዳም የተወለደ አይደለም፡፡ አንዳች ነገር ሊያሳየን ስለፈለገ እግዚአብሔር በዚህ መልክ እንዲጻፍ አደረገ፡፡ እዉነታዉ የሆነዉሔዋን በማህጸኗ ዉስጥ ሁለት ወንዶች(መንታዎች)ከተለያዩ አባቶች የተጸነሱ ነበሩ መንታዎችን አርግዛ ነበር ቃየን የተጸነሰዉአቤል ከመጸነሱ አስቀድሞ ነበር፡፡

ውስጥ ሙሉ መለያ ያንብቡ... የኤፌሶን ቤተክርስቲያን ዘመን።

ይመልከቱ... የእባቡ ዘር። ለተጨማሪ ዝርዝር።



የራዕይ መጽሐፍ ተከታታይ።
በሚቀጥለው ገጽ ላይ ይቀጥላል።
(የኒቆላዊያን አስተምህሮት።)


የክርስቶስ ምሥጢር
ተከታታይ።

የእንግሊዝኛ ጋዜጣ ድረ።

እግዚአብሔር እና ሳይንስ
ተከታታይ ኢንዴክስ።

በራእይ መጽሐፍ ላይ።

 

ጥሩ ዜናው።
ኢየሱስም ስለ ኃጢአታችን ሞቷል።

የውኃ ጥምቀት።
መንገዱ ይህ ነው.
በእርሱ ሂድ.

የመለኮት ገልጿል።

 

መልእክት ዋና ዋና ትምህርቶች።

ከተፈጥሮ በላይ ደመና።

የእሳት ዓምድ።

መቃብሩ ባዶ ነው።
እርሱ ሕያው ነው።

አርኪኦሎጂ።
ሰዶምና ገሞራ።

የመኖር ቃል ተከታታይ።

 

የእሳት ዓምድ።
የመለኮት አብራርቷል።

የማብቂያ ጊዜ ተከታታይ።

 

የኖህ መርከብ።

ወቅታዊ ምርምር።
ጋብቻ እና ፍቺ።
ክርስቲያን የእግር ጉዞ
ተከታታይ። - ምልክት።

ሚቶሎጂ። ባቢሎን የምንጭ።

የመጀመሪያው ኃጢአት።
አንድ አፕል ማለት ነው?።

በለዓም መሠረተ ትምህርት ነው።

እንደሆነ ሴት ኤልዛቤልን።

የእኛ ዕድሜ በሎዶቅያ።

 
 

የእሱ ቤተ ክርስቲያን ከኢየሩሳሌም ውጪ የሚኖሩ ክርስቶስ ነው።

የኒቆላውያንን ትምህርተ።

የፍጥሞ ራዕይ።

 

ሚስጥራዊ ባቢሎን።

ሰባት ማኅተሞች
ተከታታይ።

የመልእክታችን ዝርዝር።

የገና ተከታታይ።

  ቅዱስ መጽሐፉ እንዲህ ይላል...

የእግዚአብሔር ልጆችና የዲያብሎስ ልጆች በዚህ የተገለጡ ናቸው፤ ጽድቅን የማያደርግና ወንድሙን የማይወድ ሁሉ ከእግዚአብሔር አይደለም።

ከመጀመሪያ የሰማችኋት መልእክት። እርስ በርሳችን እንዋደድ የምትል ይህች ናትና፤

ከክፉው እንደ ነበረ ወንድሙንም እንደ ገደለ እንደ ቃየል አይደለም፤ ስለ ምንስ ገደለው? የገዛ ሥራው ክፉ፥ የወንድሙም ሥራ ጽድቅ ስለ ነበረ ነው።

1ኛ የዮሐንስ መልእክት 3:10-12


ሙሉ መጠን ሥዕሎች ወይም ፒዲኤፍ ለማውረድ ምስል ላይ ጠቅ ያድርጉ።


Acts of the Prophet.

(PDF እንግሊዝኛ)።

The Two Babylons

by Rev Alexander Hislop.
(PDF እንግሊዝኛ)።

ቻይና ውስጥ በረዶ ውስጥ አንዲት ተራራ እና የጽጌረዳን።

የእሳት በአበቦች።

የእሳት ዓምድ።
- የሂዩስተን 1950።

አንድ ፒራሚድ ዓለት ላይ ብርሃን ነው።

መብላት ፖም ሴቶች
አድርጎ ከሆነ
እነሱ እርቃናቸውን
ነበሩ መገንዘብ
ፖምቹን እንደገና
ለማለፍ ጊዜው
አሁን ነው ፡፡



መልዕክት ሃብ...ቋንቋዎን ይምረጡ. ወንድም ብራናም ነፃ መልዕክቶችን የውርድ።